አዲስ ስደተኛ በኖርዌይ
ኖርዌይ ውስጥ ለመኖር የሚፈልጉ የዉጭ ሃገር ዜጎች የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት ህጋዊ የሆነ ምክንያት ሊኖራቸው ይገባል። የአንድ ሰው መብትና ግዴታዎች የሚወሰኑት በያዘው የመኖሪያ ፈቃድ ዓይነት መሰረት ነው። ስለዚህ ሁሉም ሰዉ የሚመለከተዉን ህግ ጠንቅቆ ማወቅ ይኖርበታል።
ኖርዌይ ውስጥ የሚኖር ማንኛውም ሰው የሃገሪቱን ህጐችና ደንቦች በደንብ የማወቅ ግዴታ አለበት። በሚመለከተዉ የመንግስት አካል በሚጠየቅበት ጊዜም ትክክለኛውን መረጃ የመስጠት ግዴታ አለበት።